30/05/2026
ቴሌግራም Wallet በኢትዮጵያ የሚደረግ የክሪፕቶ ግብይት (P2P Trading) ሊያቆም ነው!
በቴሌግራም ላይ ክሪፕቶ ግብይት መድረክ የሆነው ዋሌቴ (Wallet) ከግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ከ June 2, 2026) ጀምሮ በኢትዮጵያ ብር የሚደረጉ የክሪፕቶ ግብይቶችን (P2P Trading) እንደሚያቆም አስታወቀ።
ይህ ውሳኔ የተወሰደው የሀገሪቱን የፋይናንስ ህግ መሰረት አድርጎ እንደሆነም ይፋ ተደርጓል።
ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ሁሉም በኢትዮጵያ ብር የሚደረጉ የP2P ትሬዲንግ ማስታወቂያዎች በሙሉ እንዲነሱ ይደረጋል ፤ አዲስ ማስታወቂያዎችንም Post ማድረግ እንደማይቻል ተገልጿል።
ከቀነ ገደቡ በፊት የተጀመሩ ግብይቶች በተለመደው አሰራር መሠረት መፈጸም እንደሚቻል ና ተጠቃአሚዎች በሂደት ላይ ያሉ የትሬዲንግ ስምምነቶችን በፍጥነት እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደምም ፦
- Bitget
- Binance
- Okx
- Bybit የመሳሳሉ መድረኮች በኢትዮጵያን ብር የሚደረጉ የክሪፕቶ ግብይቶች (P2P) ማቆማቸው ይታወሳል።
አሁን ደግሞ በP2P ግብይት በስፋት የሚታወቀው Telegram Wallet ከግንቦት 25,2018 በኋላ በኢትዮጵያ ብር መስራት እንደሚያቆም ታውቋል።
ቴሌግራም ዋሌትም ይሁን ሌሎች ከላይ የጠቀስናቸው በኢትዮጵያ ብር የክሪፕቶ ግብይት ለማቆማቸው እንደምያንያት የተገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ (NBE) የአቻ ለአቻ (P2P) የንግድ ልውውጥ ሕገ-ወጥ መሆኑን በመግለጹ ና ከብር ውጪ በቨርቷል ከረንሲ የሚደረጉ ግብይቶች ህጋዊ እንዳልሆኑ በቅርቡ የካቲት 27,2026 ላይ ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ በማውጣቱ እንደሆነም ተነግሯል።