Tewahido

Tewahido የእውነት አባት ምን ይላሉ

በአንድ መሠዊያ ላይ የቀረቡ ሶስቱ ወንድማማች ዲያቆናት የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች"እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።" — ኢያሱ 24:15በደቡብ ኢትዮጵያ በባስኬቶ ዞ...
21/08/2026

በአንድ መሠዊያ ላይ የቀረቡ ሶስቱ ወንድማማች ዲያቆናት የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች

"እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።" — ኢያሱ 24:15

በደቡብ ኢትዮጵያ በባስኬቶ ዞን የሚገኝ አንድ የተባረከ ቤተሰብ ለአምላኩ ያቀረበውን ድንቅ የመንፈሳዊ አገልግሎት ፍሬ የሚያሳይ ምስል የብዙዎችን ልብ በደስታና በመንፈሳዊ ቅናት እያንቀሳቀሰ ይገኛል።

በአንድ መቅደስና በአንድ ቅዱስ መሠዊያ ፊት በጋራ ቆመው ሥርዓተ ቅዳሴውን የሚያከናውኑት ሶስቱ ወንድማማቾች

1. ዲያቆን አረጋህኝ ተስፋዬ
2. ዲያቆን አሸናፊ ተስፋዬ
3. ዲያቆን ታርኩ ተስፋዬ

በአንድ ቅዱስ ማዕድ ዙሪያ በአንድነት ቆመው ፈጣሪያቸውን ሲያገለግሉ ማየት፣ የመንፈስ ቅዱስን አንድነትና የቤተሰብን እውነተኛ በረከት በግልጽ ያሳያል።

በአንድ ቤት ውስጥ ተወልደውና አድገው፣ የቅድስናውን ጥሪ በጋራ ተቀብለው ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መብቃታቸው የወላጆቻቸውን መልካም ክርስቲያናዊ ኮርቻ እና የጥበብ አስተ hisፅኦ ፍልስፍና ይመሰክራል።

ወንድማማቾች በአገልግሎት በፍቅርና በአንድነት ሲቆሙ ማየት ለአካባቢው ምእመናን ብቻ ሳይሆን ለአዲሱ ትውልድም ታላቅ አርአያና የመንፈሳዊ ህይወት ማበረታቻ ነው።

እግዚአብሔር አምላክ ለደቡብ ኢትዮጵያና ለባስኬቶ ዞን የሰጠውን ይህንን የመንፈስ ፍሬ ይባርክ፤ የአገልግሎት ዘመናቸውን ሙሉ በጸጋ፣ በፍቅርና በቅድስና ያፅናልን!

via፦ ዲያቆን አረጋህኝ ተስፋዬ
ግዮን ማለዳ

እንኳን ለቡሄ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ሆያ ሆዬ! ...የቡሄው ድምቀት  ሙልሙል ዳቦከየኮረብታዎች አናት የሚንጠሸጠሸው የጅራፍ ድምፅና ቡሄ  ውብ የልጅነት ትዝታ!ሁሌም የሚናፈቅ ውብ የልጅነ...
18/08/2026

እንኳን ለቡሄ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ሆያ ሆዬ! ...

የቡሄው ድምቀት ሙልሙል ዳቦ
ከየኮረብታዎች አናት የሚንጠሸጠሸው የጅራፍ ድምፅና ቡሄ ውብ የልጅነት ትዝታ!

ሁሌም የሚናፈቅ ውብ የልጅነት ዓለም ነው የቡሄ በዓል። የማይደበዝዝ ትዝታ የተቋጠረበት።

"ሆያ ሆዬ" ተጨፍሮ፤ ሙልሙል ዳቦ እየተገመጠ፤ በቡሄ ጎጆ በመሠባሰብ ልዩ የልጅነት ትውስታ ያጣጣምንበት ነው። ተካፍሎ የመብላት፣ የፍቅርና የእኩልነት መድረክ ኾኖ በልጅነት ልባችን ውስጥ ታትሞ ቀርቷል።

የቡሄ በዓል በተስፋ እና በደስታ የተሞላ የልጆች የመቦረቂያ ጊዜ ሲኾን የዝናቡና የጨለማው ወቅት ማለፉን፣ የብርሃንና የደስታ እንዲኹም የልምላሜ ዘመን መምጣቱን ማብሠሪያ ምልክትም ተደርጎ ይወሰዳል።

የሙልሙል ዳቦው ጣዕም፣ "የሆያ ሆዬ" ጭፈራውና የህጻንነት ንፁህ ደስታ ከዓመታት በኋላም ቢኾን ትዝታው ከሕሊና የሚጠፋ አይደለም። ወደ ልጅነት ዓለም በምናብ ይወስዳል።

የቡሄ በዓል መቃረብ በህጻናት ልብ ውስጥ የተለየ ደስታና ናፍቆት ይፈጥራል። በየመንደሩ ህፃናት ጅራፍ ገምደው ሲያኖጉ መንደሩም ክረምቱም ይደምቃል።

በቡሄ እለት በየቤቱ ልጆች እየዞሩ ሲጨፍሩም ሙልሙል ዳቦ ይሰጣቸዋል፡፡ በኮባ የተጋገረው ሙልሙል ዳቦ ልጅነትን የሚያስናፍቅ ውድ የእናቶች ስጦታ ነው። ከየትኛውም ጣፋጭ ምግብ የሚጥም በስስትና በሽሚያ በትንሿ የቡሄ ጎጆ ውስጥ የሚገመጥ ነው።

የ“ሆያ ሆዬ” ዜማ በልጆች ኮልታፋ አንደበት ሲዜም የራሱ የኾነ ልዩ ቀለምና ጣዕም አለው። ይናፈቃል። ቡሄ የልጅነታችንን ንጹህ የደስታና የፍቅር ጊዜ ደግሞ ደጋግሞ የሚያስታውሰን አይረሴ ትዝታችን ነው።

ቡሄ ሲቃረብ ከሳምንታት አስቀድሞ ጅራፍ ይዘጋጃል። ከየኮረብታዎች አናት የሚንጠሸጠሸው የጅራፍ ድምፅ ደግሞ የሐምሌና ነሐሴ ልዩ ውበት ነው። ቡሄ ፣ክረምትና ጅራፍ ልጅነታችንን ያስጌጡ ውብ ትዝታዎች ናቸው።

የደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓልአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን የሚከበረው የደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል ሐይማኖታዊ እና ባህላዊ ይዘት አለው፡፡ቡሄ የክረ...
17/08/2026

የደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን የሚከበረው የደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል ሐይማኖታዊ እና ባህላዊ ይዘት አለው፡፡

ቡሄ የክረምት ጭጋግ ተወግዶ ወደ ጸሃይ ብርሃንነትና ብሩህነት በሚሸጋገርበት ወቅት ይከበራል፤ ''ቡሄ ካለፈ የለም ክረምት" ፤ "ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት" ፤ መባሉም ለዚሁ ነው፡፡

የደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል በሐይማኖታዊ አስተምህሮው ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ተራራ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት መሆኑን የሃይማኖት አባቶች ያስረዳሉ፡፡

መጋቤ ብሉይ አዕምሮ ዘውዴ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርቲያን በመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋሪያዊ ተልዕኮ መምሪያ የስምሪት ሃላፊ ናቸው፡፡

እንደ መጋቤ ብሉይ አዕምሮ ገለጻ÷ የደብረ ታቦር በዓል በመጽሐፍ ቅዱስ ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው ፤ በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ይዞ ወደ ደብረ ታቦት ተራራ የወጣበትና በዚያም ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ነው፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ ያዕቆብ፣ ዮሃንስንና ጴጥሮስን በስጋ ከሚኖሩበት ዓለም፣ ሙሴን ከመቃብር በማስነሳት እንዲሁም ኤልያስን ከተሰወረበት ዓለም በማምጣት አንድ ላይ በደብረ ታቦር አነጋግሯቸዋል፡፡ ብርሃነ መለኮቱንም ገልጦላቸዋል ይላሉ ፡፡

ደብረ ታቦር በእየሩሳሌም የሚገኝ 572 ሜትር ከፍታ ያለው ታላቅ ተራራ ሲሆን÷ ሶስት ነገሮችን ይወክላል፤ ወንጌልን፣ ቤተክርስቲያንንና መንግስተ ሰማያትን፡፡

በዓሉ ሕያውያንና ሙታን የሚያከብሩት፤ እግዚአብሔርም የሕያውያን እና የሙታን አምላክ መሆኑን ያስረዳበት እንዲሁም ትናንት፣ ዛሬ እና ነገን ያሳየበት መሆኑን መጋቤ ብሉይ አእምሮ አስገንዝበዋል፡፡

ደብረ ታቦር በቤተክርስቲያን በረጅም ማህሌት፣ በቅዳሴ፣ በትምህርትና በሌሎች መንፈሳዊ ክንውኖች እንደሚከበር ጠቁመው÷ ከመንፈሳዊነቱ በተጨማሪ በዓሉ የአንድነት፣ አብሮነትና የመተሳሰብ ምሳሌ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን ከተለያየ ቦታ ማለትም በስጋ ከሚኖሩበት ዓለም፣ ከመቃብርና ከተሰወሩበት ዓለም በማሰባሰብ በደብረ ታቦር ተራራ አንድ ሆነውና ተስማምተው በዓሉን እንዳከበሩ አስታውሰው ÷ይህም የተለያየ የኑሮ ደረጃ፣ የተለያየ ባህልና ቋንቋ ያላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች መረዳዳትና መቻቻል እንዳለባቸው ያስተምራል ነው ያሉት፡፡

በሌላ በኩል ሙልሙል ዳቦ መስጠት፣ ችቦ ማብራት እና ጅራፍ ማጮህ ከደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል ጋር ተያይዞ የሚከናወኑ ትውፊታዊ መገለጫዎች እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡

ሙል ሙል ዳቦ ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን በገለጠ ጊዜ ብርሃን ስለሆነ የአካባቢው እረኞች/ልጆች የመሸ ስላልመሰላቸው ወደ ቤት ሳይመለሱ ቀሩ፤ በዚህ የተጨነቁ ወላጆችም ስንቅ ይዘውላቸው መሄዳቸውን ለማመላከት መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ችቦ የሚበራው ደግሞ በደብረ ታቦር ተራራ ብርሃን መገለጡን በማስመልከት ሲሆን÷ ጅራፍ የሚጮኸውም በተራራው ድምጸ መለኮት መሰማቱን ለማስታወስ ነው ይላሉ፡፡

የደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በነገው ዕለት በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ይከበራል፡፡

መልካም የቡሄ በዓል!

በመላኩ ገድፍ

✞ ​ ቡሄ በሉ /2/ ሆኦ    ልጆች ሁሉ ሆየኛማ ጌታ ሆኦ  የዓለም ፈጣሪ ሆየሰላም አምላክ ሆ ትሁት መሀሪ ሆበደብረ ታቦር  ሆ  የተገለጠው  ሆፊቱ እንደ ፀሐይ ሆ በርቶ የታየው ሆልብሱ እ...
15/08/2026

✞ ​

ቡሄ በሉ /2/ ሆኦ ልጆች ሁሉ ሆ
የኛማ ጌታ ሆኦ የዓለም ፈጣሪ ሆ
የሰላም አምላክ ሆ ትሁት መሀሪ ሆ
በደብረ ታቦር ሆ የተገለጠው ሆ
ፊቱ እንደ ፀሐይ ሆ በርቶ የታየው ሆ
ልብሱ እንደብርሃን ሆ ያንፀባረቀው ሆ

ድምጽህን ሰማና በብህሩ ደመና/2/
የቡሄው ብርሃን ለኛ መጣልን/2/

ያዕቆብ ዮሐንስሆ እንዲሁም ጴጥሮስ ሆ
አምላክን አዩት ሆ ሙሴ ኤልያስ ሆ
አባቱም አለ ሆ ልጄን ስሙት ሆ
ቃሌ ነውና ሆ የወለድኩት ሆ


ታቦር አርሞንኤም ሆ ብርሃን ታየባቸው ሆ
ከቅዱስ ተራራ ሆ ስምህ ደስ አላቸው ሆ
ሰላም ሰላም ሆ የታቦር ተራራ ሆ
ብርሀነ መለኮት ሆ ባንቺ ላይ አበራ ሆ


በተዋህዶ ሆ ወልድ የከበረው ሆ
የእግዚአብሔር አብ ልጅ ሆ ወልደማርያም ነው ሆ
ቡሄ በሉ ሆ ቡሄ በሉ ሆ
የአዳም ልጆች ሆ ብርሃንን ሆ ተቀበሉ ሆ


አባቴ ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ
እናቴ ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ
ከአጎቴም ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ
አክስቴም ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ
ተከምሯል ሆ እንደ ኩበት ሆ


የዓመት ልምዳችን ሆ ከጥንት የመጣው ሆ
ከተከመረው ሆ ከመሶቡ ይውጣ ሆ
ከደብረ ታቦር ሆ ጌታ ሰለመጣ ሆ
የተጋገረው ሆ ሙልሙሉ ይምጣ ሆ


ኢትዮጵያውያን ሆ ታሪክ ያላችሁ ሆ
ባህላችሁን ሆ ያዙ አጥብቃችሁ ሆ
ችቦውን አብሩት ሆ እንዳባቶቻችሁ ሆ
ምስጢር ስላለው ሆ ደስ ይበላችሁ ሆ


አባቶቻችን ሆ ያወረሱን ሆ
የቡሄን ትርጉም ሆ ያሳወቁን ሆ
እንድንጠብቀው ሆ ለእኛ የሰጡን ሆ
ይህን ነውና ሆ ያስረከቡን ሆ


ለድንግል ማርያም ሆ አሥራት የሆንሽ ሆ
ቅዱሳን ጻድቃን ሆ የሞሉብሽ ሆ
በረከታቸው ሆ ያደረብሽ ሆ
ሁሌም እንግዶች ሆ የሚያርፉብሽ ሆ
ሀገረ እግዚአብሔር ሆ ኢትዮጵያ ነሽ ሆ


ለሐዋርያት ሆ የላከ መንፈስ ሆ
ዛሬም ለኢትዮጵያ ሆ ጸጋውን ያፍስስ ሆ
በበጎ ምግባር ሆ እንድንታነጽ ሆ
በቅን ልቦና ሆ በጥሩ መንፈስ ሆ
በረከተ ቡሄ ሆ ለሁላችንይድረስ ሆ

ዓመት ዓውዳመት ድገም እና ዓመት ድገም እና
በጋሽዬ ቤ ድገም እና ዓመት ድገም እና
ያውርድ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ወርቅ ይፍሰስበት ድገም እና ዓመት ድገም እና
በእማምዬ ቤት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ይግባ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ማርና ወተት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ይትረፍረፍ በእውነት ድገም እና ዓመት ድገም እና

እንዲሁ እንዳላችሁ በምነት አይለያችሁ በምነት
ላመቱ በሰላም በምነት ያድርሳችሁ በምነት
ክርስቶስ በቀኙ በምነት ያቁማችሁ በምነት
የመንግስቱ ወራሽ በምነት ያድርጋችሁ በምነት
እንዲሁ እንዳለን በምነት አይለየን በምነት
ለዓመቱ በሰላም በምነት ያድርሰን በምነት
አማኑኤል በቀኙ በምነት ያቁመን በምነት
የመንግስቱ ወራሽ በምነት ያድርገን በምነት

የቅዱሳን መላክት የፃድቃን ሰማዕታት
ረድኤት በረከት ይግባ በሁሉም ቤት
በሁሉም ቤት/2/ ይግባ በረከት/2/
እንቁም በሃይማኖት ፀንተን በትጋት
የአስራት አገር በደል የሌለባት
ያቆዩልንን የአበው ቀደምት
ይገባልና ልንጠብቅ በእውነት
ባህላዊ ነው የአባቶች ትውፊት /3/

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

እናታችን ቅድስት  ኪዳነ ምህረት ከክፉ ነገር ሁሉ  ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏የእግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን ለቅዱሳኑ ከሃይማኖታቸው ጽናት ከፍጹምነታቸውና ከሥራቸው ትሩፋ...
15/08/2026

እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏

የእግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን ለቅዱሳኑ ከሃይማኖታቸው ጽናት ከፍጹምነታቸውና ከሥራቸው ትሩፋት የተነሳ በቅድስና ክብር አክብሮ ለገድላቸው እንዲሁም በተጋድሎ ላሳለፉበት ቦታ ለረገጡት አፈር ሁሉ በረከታቸው ተርፎ ዛሬ እኛ ምእመናን በየመካናቱ እምነቱን በመተሻሸት በመጠጣት ከቅዱሳኑ በረከት እንሳተፋለንል፡፡

በዘጸአት 20÷2-6 እግዚአብሔር አምላክ ለሚወዱትም ትእዛዙን ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን እንደሚያደርግ ተጽፏል፡፡ በዘዳግም 7÷12 ደግሞ “እንዲህም ይሆናል፤ ይህችን ፍርድ ሰምተህ ብትጠብቃት ብታደርጋትም፥ አምላክህ እግዚአብሔር ለአባቶችህ የማለውን ቃል ኪዳንና ምሕረት ለአንተ ይጠብቅልሃል” ይላል፡፡ ኪዳነ ምህረት፣ የምህረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡

ይህም ፍጹም ከከበሩ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የማይጠፋ የዘላለም ኪዳን የሰጠበት ዕለት መታሰቢያ ነው፡፡ ታላቁ የነገረ ማርያም መጽሐፍ እንደሚያስረዳን ጌታችን ካረገ በኋላ እመቤታችን ጌታ ወደ ተቀበረበት ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ነበር፡፡ በየካቲት 16 ቀንም ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ “ልጄ ወዳጄ ሆይ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለመሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ” እያለች ጸለየች፡፡ ጌታችንም መጥቶ ምን እንዲያደርግላት እንደምትፈልግ ጠየቀችው፡፡

ቅድስት ድንግል ማርያም በስሟ ለሚማጸኑ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጠየቀችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በአባቴ፣ በራሴና በመንፈስ ቅዱስ ማልሁልሽ ቃል ኪዳንም ገባሁልሽ አላት፡፡

ይህን የማያልፍ የምህረት ቃል ኪዳን ስለገባላትም ዕለቱ ኪዳነ ምሕረት የምሕረት የይቅርታ መሐላ፣ ውል፣ ስምምነት፣ ተብሎ በዝማሬ፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ ምዕመናንም ዘወትር በረከትን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ይቀበላሉ፡፡ ገዳማውያንም ይህን ቃል ኪዳኗን አስበው ዘወትር ምህረትን አማልጂ ይሏታልና ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦
ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-
0918077957 ወይም 0938644444

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

 #እያደር አዲስ 🤔🤗 የአንገት መስቀልን ስረግም የሰማነውን የመብራት ፖል የሚያክል ተሸክሞ አየነውፈጣረ ማስዋል ይስጣችሁ ።
15/08/2026

#እያደር አዲስ 🤔🤗 የአንገት መስቀልን ስረግም የሰማነውን የመብራት ፖል የሚያክል ተሸክሞ አየነው
ፈጣረ ማስዋል ይስጣችሁ ።

ጾመ ፍልሰታ 🙏 ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን🙏ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ ማረግ፣ ወደላይ መውጣት የሚ...
14/08/2026

ጾመ ፍልሰታ 🙏

ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን🙏

ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ ማረግ፣ ወደላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ይይዛል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች” በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል።

ይህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከተወሰኑት ሰባቱ አጸዋማት ለዓመቱ የመጨረሻው ጾም ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ከኖረች በኋላ ጥር 21 ቀን 49 ዓመተ ምሕረት ዐርፈለች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና፣ ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል፤ እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው ብለው ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡

እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡ መላእክት የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ በስምንተኛው ወር በነሐሴ ሐዋርያት ቅዱስ ይህን በረከት አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው ከነሐሴ 1 እስከ 14 ሁለት ሱባዔ ይዘው ከጌታችን ተቀብለው በጸሎትና በምህላ ቀበሯት።

ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወጥቶ ነበርና ሲቀብሯት አልተገኘም። እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጇ ከሙታን ተነሥታ ስታርግ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ አገኛት። በዚህን ጊዜ ትንሣኤዋን ሌሎች ሐዋርያት አይተው እርሱ የቀረበት መስሎት “ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ራሱን ከደመና ላይ ሊወረውር ቃጣው።

እመቤታችን ከእርሱ በስተቀር ትንሣኤዋን ያየ አለመኖሩን ነግራ ግን ቶማስን አፅናናችው፡፡ ለምስክርነት እንዲሆንም በቀብሯ ጊዜ የነበረውን ሰበኗን ሰጥታው አረገች። ቅዱስ ቶማስም ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ አላቸው፡፡ እነርሱም አግኝተን ቀበርናት አሉት፡፡

እርሱም “ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ ይህ እንዴት ይሆናል?” ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ “ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ” ብሎት ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ “አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ” ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸውና ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡

በዓመቱም ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን ብለው ከነሐሴ አንድ ጀምረው ሱባዔ ገቡ። ነሐሴ 16 ጌታችን እመቤታችንን አምጥቶ ሐዋርያትን ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ገዳውያን ይህን የጾም ወቅት ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመጸለይ ያሳልፉታል፡፡ ገዳማቸውን

"ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች በዋዛ ያደግሽ አይደለሽም በቅድስና እና በንጽህና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ"    ቅዳሴ ማርያም
14/08/2026

"ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች በዋዛ ያደግሽ አይደለሽም በቅድስና እና በንጽህና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ"

ቅዳሴ ማርያም

ካለን ላይ በማካፈል ለተቸገሩ እንድረስ፣የበረከት ስራን እንስራ🙏ታላቁ ጻድቅ አባት አባ ሣሉሲ ዜና ሕይወታቸው እጅግ ከሚያስገርሙ ገዳማውያን አንዱ ናቸው። መጽሐፈ ስንክሳር እንደሚገልጸው የዘመ...
14/08/2026

ካለን ላይ በማካፈል ለተቸገሩ እንድረስ፣የበረከት ስራን እንስራ🙏

ታላቁ ጻድቅ አባት አባ ሣሉሲ ዜና ሕይወታቸው እጅግ ከሚያስገርሙ ገዳማውያን አንዱ ናቸው። መጽሐፈ ስንክሳር እንደሚገልጸው የዘመነ ከዋክብት ፍሬ ከሚባሉት ጻድቃን አንዱ ሲሆኑ በነበሩበት ገዳም የሚታወቁት ግን 'የማይጾመው፣ የማይጸልየው፣ ሥራ ፈቱ መነኩሴ' በሚል ነበር።

ገዳሙ ውስጥ ከሚኖሩ መነኮሳት መካከል አንድም ቀን ቢሆን አባ ሣሉሲ ሲጸልዩና ሲሰግዱ ያያቸው የለም። ሁሌ ብቻ እንደ ሞኝ ቁጭ ብለው ያኝካሉ። በዚህ ምክንያትም ሥጋ ወደሙን ወስደው አያውቁም።

አንድ ቀን ግን በገዳሙ በዓል ላይ አበምኔቱና መነኮሳቱ መከሩ። "አባ ሣሉሲን አሥረን አውለን ቢያንስ ለቁርባን እናብቃቸው።" ሲሉ ወሰኑ። በውሳኔው መሠረትም በጧት ሒደው ጻድቁን አሠሯቸው።

አባ ሣሉሲም "ፍቱኝ ቁርሴን ልብላበት?" ሲሉ ተቆጡ። መነኮሳቱ ግን "ሳትቆርብ አንለቅህም።" አሏቸው። በዚህ ጊዜ ጻድቁ ቆባቸውን አውልቀው "እመቤቴ የሰው ልጅስ ጨካኝ ነው። አንቺ ግን ርኅርኅት ነሽ።" ብለው በቆባቸው ግድግዳውን ቢመቱት ለሁለት ተሰነጠቀ።

እርሳቸውም ሁለት ክንፍ አውጥተው በረው ተሰወሩ። ባዩት ነገር የደነገጡ መነኮሳት እያለቀሱ ሦስት መቶ ጊዜ "እግዚኦ....." አሉ። በዚህ ጊዜ የጻድቁን ቆብ አገኙ። በዚህች ቆብም አጋንንትን አሳደዱ ተአምራትንም ሠሩ።

አባ ሣሉሲ ግን ሃያ አራት ሰዓት ሙሉ በተመስጦ በልባቸው ስለሚጸልዩና ይህ ቅድስናቸው እንዳይታወቅ ነበር የሚጥሩት፡፡ በጧት ተነስተው የሚያኝኩትም ደረቅ ሣር እንጂ ምግብ አልነበረም። ከውዳሴ ከንቱ መራቅ ማለት ይሔው ነው።

ስንቶቻችን ጥቂቷን በጎነታችን ሰው ሁሉ እንዲያውቅልን ስንጥር ገዳማውያን ግን ጤዛ ልሰው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ግርማ ሌሊቱን ጸብአ አራዊቱን ታግሰው ሀገርንና ሕዝብን ሌት ተቀን በጸሎት ሊያስምሩ እየተጉ መንፈሳዊ ጸጋና ክብር ሲያገኙ ትሕትናቸው ይበልጥ ከፍ ይላል፡፡

“ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም” በከባድ ንፋስና ዝናብ ምክንያት ቤተ መቅደሱ ፈርሶ ይገኛል፣ መነኮሳቱም በድርቅና በርሃብ ከባድ ፈተና ውስጥ ሆነው ድጋፋችንን እየጠበቁ ነውና የድጋፍ እጃችንን እንዘርጋላቸው።

በረሃብ ውስጥ መኖር የዕለት እንጀራን ብቻ ማጣት ሳይሆን ጤናን፣ ክብርንና ተስፋን የሚፈታተን አስከፊ ሕይወት ነውና ካለን ላይ በማካፈል ገዳማዊያኑን እንርዳ፣ለነፍሳችንም ስንቅን እንያዝ።

ድጋፍ ለማድረግ፡-
ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡- 1000766349227

አቢሲንያ ባንክ ፡- 262281132

ለበለጠ መረጃ:-
0944672222 ወይም 0916106921

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

Address

No
Awassa

Telephone

+251937826061

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tewahido posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tewahido:

Shortcuts

Share