30/01/2026
👉👉👉ከነገ ጀምሮ የፕላስቲክ ከረጢቶችን ስስ ፌስታል ይዞ የተገኘ ግለሰብ ከ2 ሺህ ብር ጀምሮ ይቀጣል
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከነገ ጥር 23 ጀምሮ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚጠቀሙ፣ የሚያመርቱና ወደሀገር ውስጥ የሚያስገቡ አካላትን መቅጣት ሊጀመር መሆኑን አሳውቋል።
ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ማምረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባትና ይዞ መገኘት የሚከለክለው አዋጅ ከሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጸደቀ ቢሆንም፣ ባለስልጣኑ የስድስት ወራት የሽግግር ጊዜ ሰጥቶ መቆየቱን ገልጿል።
የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ሀላፊ እና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተሾመ አቡኔ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት እገዳው ሁሉንም አይነት ፌስታሎች (ጥቁር፣ ነጭ፣ ትናንሽ እና ትልልቅ) እንደሚያጠቃልል እና በእጁ ፌስታል ይዞ የተገኘ ከነገ ጀምሮ እንደሚቀጣ ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የህግ አስከባሪዎች አስፈላጊውን ስልጠና ወስደው በየአካባቢው ለክትትል ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ቅጣቱ ይጀመራል ተብሏል፡፡
ህጉን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ በእጅ ይዞ ለተገኘ ግለሰብ፡ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር ቅጣት። ለአምራቾች፣ አከማችዎች እና አከፋፋዮች፡ ከ50,000 እስከ 200,000 ብር ቅጣት እና እስከ አምስት አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚያስቀጣ አቶ ተሾመ አቡኔ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
Via ዳጉ_ጆርናል